ታላቁ እያሱ ግምብ
ታላቁ እያሱ ግምብ (አድያም ሰገድ ግምብ)፣ በንጉሱ ታላቁ እያሱ ዘመን ተገንብቶ በ1677 (ዘመነ ማቲዎስ) የተጠናቀቀ ነበር። የአናጢዎች መሪ ወልደ ጊዮርጊስ ግምቡን የሰራው ሲሆን በጊዜው ከጠቢቡ ሰለሞን ቤት የብለጠ ያምር ነበር በመባል የተደነቀ ነበር። [1] የግምቡ ጣሪያ በወርቅና በከበሩ ደንጊያወች ያጌጠ ነበር። ወለሎቹም ከዝሆን ጥርስና ከቅጠላቅጥል ጌጦች የተሰራ ነበር።[2] ግምቡ በ2ኛው የዓለም ጦርነት ጊዜ በእንግሊዝ የአውሮፕላን ቦምብ ድብድባ የተጎዳ ቢሆም አብዛኛው ክፍሉ ግን አሁን ድረስ ሳይፈርስ ይገኛል።

ታላቁ እያሱ ግምብ፣ 1894ዓ.ም. (አንድ አንድ ክፍሎቹ በሁለተኛው የአለም ጦርነት ሳይፈርሱ)
*ግምጃ ቤት ማርያም
*ፋሲል ቤተክርስቲያን
*ድልድይ
*ቋል (ጋብቻ)ቤት
*እልፍኝ ጊዮርጊስ
አዋጅ መንገሪያ*
ክረምት ቤት*
*አዋጅ ነጋሪ
*ጃን ተከል ዋርካ
*ሰሜን
አደባባይ ተክለ ሃይማኖት
ታላቁ እያሱ የደብረ ብርሃን ሥላሴንና ሌሎች ፯ ቤተክርስቲያኖችን በመገንባት በተጨማሪ ይታወቃል።

የታላቁ እያሱ ግምብ
ማጣቀሻ
- Budge,( 1928) pp. 409
- ሪቻርድ ፓንክኸርስት፣ The Ethiopians: a history፣ ገጽ 111
This article is issued from Wikipedia. The text is licensed under Creative Commons - Attribution - Sharealike. Additional terms may apply for the media files.