ቡልጋ

ቡልጋአማራ ክልልሰሜን ሸዋ ዞን ውስጥ የሚገኝ ወረዳ ሲሆን አቀማመጡ በአብዛኛው ከቆላ እስከ ወይና ደጋ ነው። የወረዳው አስተዳደር ፣ የሀገረ ማርያም ከሰም ወረዳ ሲባል ሀገረ ማርያም (ሾላ ገበያ ) የሚባለው የገጠር ከተማ ላይ ይገኛል።

በወረዳው ውስጥ የዳግማዊ ምኒልክ ምሽግና የመሳሪያ ግምጃ ቤት የነበረችው ኮረማሽ የምትገኝበት ወረዳ ሲሆን እንዲሁም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሃይማኖት ተከታዮች እንደሚያውቁት ቡልጋ የብዙ ኢትዮጵያውያን ቅዱሳን እና ቅዱሳት የትውልድ አገርም ነች።

፲፱፻፺፱ ዓ/ም የሕዝብ ቆጠራ ውጤት እንደሚያመለክተው በወረዳው ውስጥ ፶፭ ሺህ ፪፻፩ ሰዎች ሲኖሩ የወንዶች ብዛት ፳፰ ሺህ ፫፻፸፭ እና ሴቶች ደግሞ ፳፮ ሺህ ፰፻፳፮ እንደሆኑ ይጠቁማል። ከነኚህ ቡልጎች ፶፫ ሺህ ፲፭ቱ ሰዎች የገጠር ነዋሪዎችና በግብርና የተሠማሩ አርሶ አደሮች እንደሆኑ ያረጋግጣል።[1]

የታወቁ የቡልጋ ተወላጆች

  • ቅድስት ክርስቶስ ሰምራ- ቅዱስጌ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እምነት በመልአኩ ቅዱስ ሚካኤል ዕርዳታ ብዙ ሺህ ነፍሳትን ከሲዖል ያወጣች
  • አክሊሉ ሀብተ-ወልድ ( ፀሐፌ ትዕዛዝ ) ዲፕሎማት፣ አምባሳዶር፣ የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት የውጭ ጉዳይ፤ የጽሕፈት ሚኒስቴር፣ ጠቅላይ ሚኒስቴር
  • ተስፋ ገብረ ሥላሴ የፊደል ገበታን የሰሩ የዕውቅት አባት
  • ሎሬት ዶ/ር መላኩ ወረደ የAlternative Nobel Prize ተሸላሚ ሳይንቲስት
  • ጌታቸው በቀለ - ቅንበቢት የኢ.ን.ነ.መ. ሚኒስቴር፣ አምባሳዶር
  • [አርበኛ እና የባህል ሐኪም ማሞ ኃይሌ ዘብሔረ ቡልጋ ከሰም]

ዋቢ ምንጮች

  1. Summary & Statistical Report of the 2007 Population & Housing Census, FDRE Population Census Commission
This article is issued from Wikipedia. The text is licensed under Creative Commons - Attribution - Sharealike. Additional terms may apply for the media files.