ሙቀት
ሙቀት በተፈጥሮ ህግ ጥናት ከአንድ ቁስ ወደ ሌላ ቁስ ያለምንም ስራ አቅም ሲተላለፍ ማለት ነው። ባጭሩ ለማስረዳት፣ አንድ ሰው ትልቅ ድንጋይ ወደላይ ቢያነሳ በዲንጋዩ ላይ ስራ ሰርቷአል ምክንያቱም የሰውየው ጉልበትና ድንጋዩ የተጓዘበት አቅጣጫ አንድ አይነት ስለሆነ። እንግዲህ ድንጋዩ ከፍተኛ ቦታ ላይ ሰለሆነ ያለው ቢለቀቅ ስራ ሊሰራ ይችላል፤ ይህም አቅም ከሰውየው ወደ ድንጋዩ ስራ ተላልፏል ማለት ነው። ለአቅሙ መተላለፍ ስራ ስለተሰራ ትልልፉ ሙቀት አይባልም። ባንጻሩ ድንጋዩን ፀሐይ ላይ ብንተወው እየጋለ ይሄዳል። ይህ ግለት ውሃ እላዩ ላይ ጠብ ቢልበት በማትነን በውሃ ላይ ስራ መስራት ይችላል። ይህ የሚያሳየው አቅም ከፀሐይ ወደ ድንጋዩ መተላለፉን ነው። ነገር ግን ፀሐዩዋ ድንጋዩን ስላላንቀሳቀሰችው ስራ አልሰራችበትም። ስራ ሳይሰራ የሚደረገው የአቅም ልውውጥ ሙቀት ይባላል።
This article is issued from Wikipedia. The text is licensed under Creative Commons - Attribution - Sharealike. Additional terms may apply for the media files.